በለሚ ኩራ ክ/ከተማ አስተዳደር መጪውን የጥምቀት በዓል በስኬት ማክበር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደረገ።
በዓለም የማይዳሰሱ ቅርስነት የተመዘገቡ እና የጋራ የወል ሀብታችን ከሆኑ የአደባባይ ሁነቶች መካከል ነው የጥምቀት በዓል። ለዘመናት በድምቀት በተለያዩ ሀይማኖታዊና ባህላዊ ክንዋኔዎች ደምቆ የሚከበረውን ይህንን የአደባባይ በዓል ከለውጡ ማግስት ባህረ ጥምቀት ከባቢዎች የበለጠ ተውበው እና አምረው ለበዓሉ ታዳሚዎች ጥሩ የበዓል ድባብ መፈጠር ጀምረዋል።
ይህን ደማቅ የአደባባይ በዓል ሀይማኖታዊና ባህላዊ እሴቱን እንደጠበቀ ይከበር ዘንድ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሠሩ ሲሆን ዝርዝር ተግባራት በማስፈፀሚያ ዕቅድ ተካተው በሂደቱ ዙሪያ የከተማ ደጋፊ አመራሮች በተገኙበት ከክ/ከተማው ጠቅላላ አመራር ጋር ውይይት ተደርጓል።
በውይይት መረሀ ግብሩ የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች ልማት አሰተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወ/ጊዮርጊስ
እንደተናገሩት ”በዓሉ የሁላችንም የጋራ ሀብታችን መሆኑን በመረዳት ፍፁም ሰላማዊ ድባብ እንዲከበር ሁሉም የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ያሳሰቡ ሲሆን ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በሚሠራበት ሁኔታ ላይም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
የክ/ከተማችን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ደቻሳ በበኩላቸው ”እንደ ክ/ከተማ በዓሉን በተለመደው ደማቅ ሁኔታ ለማክበር አስቻይ ሁኔታዎችን ለይተን ሊገጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶችን ከግምት ውስጥ ያስገባ በቂ ቅድመ ዝግጅት እና ከሀይማኖቱ አባቶች እና የደብር አስተዳደሮች ጋርም ተግባቦት መፈጠሩን እና በጋራ ለመስራት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራ መሰራቱን ነው ያብራሩት።
የክ/ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ፋንቲሁን ለማንቾ ”እንደ ክ/ከተማው ከሀይማኖት ተቋማት ጋር ተቀራርቦ የመሥራት ዘለግ ያለ ልምድ ያለ መሆኑን አንስተው በተለይም በእንዲህ ያሉ የበዓል ወቅቶች ተናቦ ተቀራርቦ የመሥራት ልምዳችንን አጠናክርን የምንሄድበት ከአጎራባች ክ/ከተሞችና የሸገር ሲቲ ከባቢዎች ጋርም በመናበብ በቅንጅት የሚሠራ መሆኑና የከተመ ደጋፊ አመራር አቅም ደምሮ በመጠቀም በጠንካራ የአመራር ስምሪትና ድጋፍ አግባብ በዓሉ ድምቀቱንና ሰላማዊነቱን እንደጠበቀ እንዲከበር በቂ የቅድመ ዝግጅት ስራ መሠራቱን ነው የገለፁት።










